|
መች ገባና ወጣሁ ይላል? አቶ ሙሴ ተገኝን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የተሰጠ መግለጫ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ኢትዮ ሚዲያ በተባለውና የትግራዩ ተወላጅ አቶ አብርሃ በላይ በሚያስተዳድረው ድረ ገጽ አማካይነት አቶ ሙሴ ተገኝ በድርጅታችን ላይ የከፈተውን ዘመቻ በተመለከተ ምላሽ ላለመስጠት ያደረግነውን ጥረት ወገን ሁሉ ይረዳዋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ነገር ግን አቶ ሙሴ ተገኝ በጥቂት የአካባቢው ሰዎችና ጸረ ኤርትራ ህዝብ ጭፍን አመለካከት ባለቸው ግለሰቦች እየታገዘ በየዕቁብ ቤቱ ሳይቀር የከፈተው ጥቃት እየጨመረ በመምጣቱና የግለሰቡ ጉዞ ያበሳጫቸው ወገኖችም ለምን ምላሽ አይሰጠውም በሚል ባቀረቡልን ተደጋጋሚ ጥያቄ መሰረት ይህን መግለጫ እንድናወጣ ተገደናል። አቶ ሙሴ ተገኝ ወይንም በተለምዶ አጠራር ፕሮፌሰር ሙሴ ሰሞኑን ከኤርትራ ለቀን ወጥተናል በማለት ራሱን እንደ ኢህ አግ አባልና መሪ በመቁጠር የህይወት መስዋዕትነትን ዛሬም እየከፈለ ባለፈው አርበኛ ሰራዊት ደም መቀለዱን ስንሰማ የተሰማን ስሜት አስቆጪ እንደሆነ መግለጽ የተገባን ይሆናል። |
|
Read more...
|
|
ወጣቱ በወያኔ አፈና ምክንያት ለስደት እየተዳረገ መሆኑ ታወቀ! |
|
የአገራችን ኢትዮጵያ ወጣት በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ ከፍተኛ እንግልት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፣ በአምባገነኑ አገዛዝ ሆድ አምላኪ ስግብግቦች የሀገርና የወገን ብልፅግና ሞተር የሆነው ወጣቱ ትውልድ በጎጠኛው ስርአት እንደጠላት ከመታየቱም በላይ የህዝቡን ኑሮ ለመስማት በሚያደርጋቸው የትኛውንም አይነት እንቅስቃሴ በህዝብ ደም በጠገቡ እብሪተኞች አናቱን በጥይት አረር ከመነደል አልዳነም፣ እንደሚታወቀው በጎንደር አካባቢ በከፍተኛ ሁኔታ የሚመረተው የማሽላና የሰሊጥ ምርት የጉልበት ስራ ለመስራት ከአራቱም አቅጣጫ የአገራችን ኢትዮጵያ ነዋሪዎች ወደዚህ አካባቢ በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች እንደሚተሙ ይታወቃል፣ በጉልበት ስራ ራሳችንና ቤተሰባችንን እናሳድጋለን ብለው ከቀያቸው ወደ ሰሜኑ ክፍል ያመሩ ኢትዮጵያውያን አላማቸውን ለማሳካት ደፋ ቀና ቢሉም እንዃን የወያኔው ግብዝ አሸርጋጆች ጋሬጣ ሆኖባቸዋል፣ |
|
Read more...
|
|
ወያኔ የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎችን በእብሪት እያፈናቀለ ይገኛል |
|
በሰሜን ጎንደር አርማጭሆ ልዩ ስሙ አብደራፊና አብረሃጅራ አካባቢ ወያኔው ቅጥ የለሽ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ታወቀ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በያዝነው ዓመት በወያኔው ላይ እያሳረፈ ያለው ጡጫ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያየለ በመምጣቱ ስጋት የገባው የወያኔው ቡድን በንፁሃኑ የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎችን በእብሪት እያፈናቀለ ይገኛል፣ የኢሕአግ የሚዲያ ክፍል ዘጋቢ ከስፍራው እንዳስታወቀው ።- በአገዛዙ ሚሊሻ፤ ልዩ ሃይልና መከላከያ ሃይላት በአርበኛው የፈረጠመ ክንድ መደቆሳቸው ቁጭት የፈጠረባቸው የአምባገነኑ ስርዓት ቅጥረኞች የአካባቢውን ነዋሪዎች ሁሉ የኢሕአግ ደጋፊዎች ናችሁ ፤ ስንቅ ታቀብላላችሁ፤ መንገድ ትጠቁማላችሁ ፤ መረጃ ታቀብላላችሁ ፤ አርበኞችን ትሸሽጋላችሁ …ወዘተ በማለት የቅልብ ጦሩ ሰለባ አድርጓቸዋል፣ |
|
Read more...
|
|
ወያኔ የራሱን ካድሬዎች ሳይቀር ከአርበኞች ግንባር ጋር በተያያዘ ለእስር እየዳረጋቸውነው |
|
ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ጋር በተያያዘ የመተማ ወረዳ ነዋሪዎች በወያኔ የደህንነት ሃይሎች እየታመሱና ለእስር እየታደረጉ መሆኑ ታወቀ። የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር እያደረገ ባለው የመረረ ሕዝባዊ ተጋድሎና እያስመዘገበ ባለው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ድል የሕዝቡን የስር ዓት ለውጥ ስሜትና መነሳሳትን እንደፈጠረ በተደጋጋሚ መዘገባችን የሚታወስ ነው። በዚህም መሰረት ስጋትና ጭንቀት የገባው የወያኒው ቡድን እየፋመ የሚገኘውን የሕዝቡን የለውጥ መነሳሳት ስሜት ለማቀዝቀዝና ሕዝባዊ የአርበኝነት ትግሉን ከሕዝብ ለመነጠል የተለመደውን የማዋከብና የእስር ዘመቻውን ሰሞኑን በመተማ ነዋሪ ሕብረተሰብ ላይ ማነጣጠሩ ከቦታው የደረሰን መረጃ እጋለጠ። |
|
Read more...
|
|
የኢሕአግ የዘመቻ ደምመላሽ ሠራዊት ወታደራዊ ጥቃት እየተፋፋመ ይገኛል፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የዘመቻ ደምመላሽ ሰራዊት በሰሜን ጎንደር ላይ አርማጭሆ ዶጋው ልዩ ስሙ ጉርማጭት በተባለ አካባቢ ላይ በታህሳስ 21- 2004 ዓ.ም በመቶ አለቃ ገበየሁ የሚመራው ልዩ ሃይል ጋር በተካሄደ ውጊያ 9 የወያኔ ልዩ ሃይል ታጣቂዎች በመግደልና 16 በማቁሰል ከባድና ቀላል መሳሪያዎችን ከነ መሰል ጥይቶቻቸው ጋር መማረኩን የኢሕአግ ወታደራዊ መምሪያ ከስፍራው አስታወቀ፣ የኢሕአግ ወታደራዊ መምሪያ ጨምሮ እንደገለፀው፦ በአካባቢው ( በስፍራው) የዘመቻ ደምመላሽ ሰራዊት በተከታታይ እያካሄደ የሚገኘው ድንገተኛ ወታደራዊ ማጥቃት እርምጃ በወያኔ የመከላከያ ፤ የሚሊሻና የልዩ ሃይል…. ታጣቂዎች ዘንድ የውጊያ ሞራል መላሸቅ እና የአርበኛው የጀግንነት በትር የአገዛዙን ታጣቂዎች አንገት የሚያስደፋ ሆኖ መገኘቱን ለአገዛዙ ቅልብ ጦር ቅርበት ያላቸው ወገኖች ገለፁ፣  |
|
Read more...
|
|
የዘመቻ ደምመላሽ የኢህአግ ሠራዊት በሰሜን ጐንደር ወልቃይት ልዩ ስሙ ሶረቃ በተባለ ቦታ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀመ።። የዘመቻ ደምመላሽ የኢህአግ ሰራዊት የታጠቀ ሀይሉን መከታ አድርጐ ህዝብን እያወደመ የሚገኘውን የወያኔ ቡድን ፊት ለፊት በመጋፈጥና አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ያለውን ጥልቅ ፍቅር በተግባር የተደገፈ ተጋድሎ በማካሄድ የዘመቻ ደምመላሽ የኢህአግ ሠራዊት የወገን ደራሽ መሆኑን በተከታታይ በሚያደርገው እልህ አሥጨራሽ የፀረ-ወያኔ ፍልሚያ በማስመስከር ላይ ይገኛል።። |
|
Read more...
|
|
የዘመቻ ደምመላሽ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት በሰሜን ጎንደር ላይ አርማጭሆ ልዩ ስሙ አሸሬ በተባለ ቦታ ጥቃት ፈፀመ፣ የዘመቻ ደምመላሽ የኢህአግ ሠራዊት ከወያኔ ቅጥረኛና ምንደኛ የመከላከያና የልዩ ሃይል ቡድን ጋር የጀመረውን የማጥቃት ዘመቻ ከመቸውም ጊዜ በላይ አጠናክሮ በመቀጠል ሕዳር 13 ቀን 2004 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ላይ አርማጭሆ ልዩ ስሙ አሸሬ በተባለ ቦታ ባደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ በማድረስ አኩሪ የሆነ ወታደራዊ ድል መጨበጡ ታወቀ፣ |
|
Read more...
|
|
የዘመቻ ደምመላሽ አካል የሆነው የኢሕአግ ሠራዊት ወታደራዊ ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል፣ ከወራት በፊት የተጀመረው የዘመቻ ደምመላሽ ሁሉ አቀፍ የወታደራዊ፤ የፖለቲካ፤ የማደራጀት፤ የዲፕሎማሲ እንዲሁም የፕሮፓጋንዳ አገርና ሕዝብ የመታደግ ታሪካዊና አኩሪ ተጋድሎ አንዱና ዋነኛው የወታደራዊ ማጥቃት እየተፋፋመ ይገኛል፣ በህዳር 6-2004 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር አርማጭሆ ልዩ ስሙ ስናር በሚባል አካባቢ የዘመቻ ደምመላሽ ስያሜ አንግቦ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር /ኢሕአግ/ ሰራዊት ወያኔው በአዲስ መልክ ያደራጀው ልዩ ሃይል የተሰኘው ታጣቂ ሃይል ጋር በተካሄደ ውጊያ 6 ገድሎ 12 ያቆሰለ ሲሆን፦ 7 ክላሽንኮፍ ጠበንጃ ከነ መሰል ጥይቶቹ ጋር የግሉ አድርጓል፣ |
|
Read more...
|